የስራ አመራር ቦርድ አዲስ ተሿሚዎች

የተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 6, 2011 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ የመረጧቸውን 4 አዳዲስ አባላትን ሹመት አፅድቋል። ተሿሚዎቹ ብዙወርቅ ከተተ፣ ውብሸት አየለ፣ ዶ/ር አበራ ደገፋ እና ዶ/ር ጌታሁን ካሳ ናቸው። ከእነዚህ አዳዲስ የስራ አመራር ቦርድ አባላት በተጨማሪ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ብርቱካን ሚደቅሳም በኃላፊነታቸው እንዲቀጥሉ የተወካዮች ምክር ቤት ወስኗል። የሰኔ ስድስቱን ሹመት እና ውሳኔ 17 የፓርላማ አባላት ተቃውመውታል።