የምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ አዲስ ተሿሚ

የካበተ የዳኝነት ልምድ ያላቸው አቶ ውብሸት አየለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድን በምክትል ሰብሳቢነት እንዲመሩ ተሹመዋል። ከአምስቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር አባላት ሁለቱ ሴቶች ናቸው ፦ ብዙወርቅ ከተተ እና ሰብሳቢዋ ብርቱካን ሚደቅሳ። ዶ/ር አበራ ደገፋ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከ20 ዓመታት በላይ ሲያስተምሩ የቆዩ ሲሆን በተመሳሳይ ዶ/ር ጌታሁንም በዩኒቨርስቲ የህግ መምህር ነበሩ። ዶ/ር ጌታሁን በማማከር ስራም ሰፊ ልምድ አላቸው።