




የካበተ የዳኝነት ልምድ ያላቸው አቶ ውብሸት አየለ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድን በምክትል ሰብሳቢነት እንዲመሩ ተሹመዋል። ከአምስቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር አባላት ሁለቱ ሴቶች ናቸው ፦ ብዙወርቅ ከተተ እና ሰብሳቢዋ ብርቱካን ሚደቅሳ። ዶ/ር አበራ ደገፋ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከ20 ዓመታት በላይ ሲያስተምሩ የቆዩ ሲሆን በተመሳሳይ ዶ/ር ጌታሁንም በዩኒቨርስቲ የህግ መምህር ነበሩ። ዶ/ር ጌታሁን በማማከር ስራም ሰፊ ልምድ አላቸው።




