Sample Category Title

ምርጫ 2018

የ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀምራል

የ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ነገ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀምራል። ምዝገባው በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደሮች እንዲሁም በሐረሪ ክልል ሙሉ በሙሉ በዲጂታል የሚከናወን ሲሆን በአፋር ክልል ደግሞ ከዚህ በፊት በተለመደው በእጅ ወይም በማኑዋል የሚከናወን ይሆናል። በተቀሩት ክልሎች የመራጮች ምዝገባው በዲጂታል እና በማኑዋል አማራጮች ይካሄዳል። የዲጂታል ምዝገባው በሁለት አይነት አማራጭ የሚከናወን እንደሆነ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። አንደኛው “ምርጫዬ” የተሰኘውን የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም መራጮች በራሳቸው ምዝገባውን የሚያከናውኑበት ነው ሲሆን ሁለተኛው አማራጭ መራጮች አቅራቢያቸው በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት በምርጫ አስፈጻሚዎች እገዛ በታብሌት የሚያከናወን ነው። ምርጫ ቦርድ ባወጣው የግዜ ሰሌዳ መሰረት የመራጮች ምዝገባ እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ላይ ጥላ ያጠላው የጸጥታ ጉዳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቁሳቁሶች ዝግጅት እና የምርጫ አስፈጻሚዎችን ሥልጠና መጠናቀቅን ተከትሎ የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ከቅዳሜ የካቲት 28 ቀን ጀምሮ እንደሚከናወን አስታውቋል። ሆኖም፣ በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ያለው የጸጥታ ችግር የምርጫው ሂደት ላይ ጥላ ያጠላ ጉዳይ ሆኗል። የምርጫ ባለድርሻ አካላት፣ በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው የጸጥታ ሁኔታ አካታችና ፍትሃዊ ምርጫን ለማካሄድም ሆነ ተያያዥ የፖለቲካ እንቅስቃሴን ለማድረግ እክል እንደሆነባቸው ይጠቁማሉ። የተለያዩ ዘገባዎች በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያለው የጸጥታ ጉዳይ አሁንም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑንና ምርጫን ለማካሄድ አዳጋች እንደሆነ ይጠቁማሉ። በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል እጅግ ብዙ ያልተፈቱ የጸጥታና ተያያዥ ጥያቄዎች መኖራቸው፣ በክልሉ በተያዘለት ቀነ ገደብ ምርጫ እንደማይካሄድ የሚጠቁሙ ናቸው። በተጨማሪም በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች አሁንም በመንግሥትና በታጠቁ ኃይሎች መካከል ግጭቶች መኖራቸው ምርጫው በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች መካሄዱ ላይ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል። ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ እና የቦርዱ ዝግጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባሳለፍነው ወር መባቻ ሀገራዊ ምርጫን እና የጸጥታ ጉዳዮችን አስመልክቶ የክልል መንግሥታት ርዕሰ መስተዳደሮች፣ የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ የጸጥታ ተቋማት...

ነእፓ ራሱን “ዕጩ መንግሥት” አድርጎ እንደሚቆጥር የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ ገለጹ

በመጪው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለፌደራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ወደ 1,500 የሚጠጉ ዕጩዎችን ያቀረበው የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)፤ ራሱን “ዕጩ መንግሥት” አድርጎ እንደሚቆጥር የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ነቢሃ መሐመድ ገለጹ። ነቢሃ በተለይ ለ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደገለጹት፤ ፓርቲው “ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት” በሚል መርህ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ራዕዩን እውን ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል። ጠንካራ ሀገርና መንግሥት መገንባት የፓርቲው ዓላማ መሆኑን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ይህን እውን ለማድረግ ምርጫ ወሳኝ በመሆኑ ፓርቲው “በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤታማ ለመሆን የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን በተቀናጀ መልኩ እያከናወነ ይገኛል” ሲሉ አክለዋል። ፓርቲው ለምርጫው ይረዳው ዘንድ የምርጫ ስትራቴጂ አዘጋጅቶ ይፋ ማድረጉንም ነቢሃ ጠቁመዋል። መሰል የምርጫ ስትራቴጂ “ከዚህ ቀደም ተዘጋጅቶ አያውቅም ወይም አልተለመደም” ያሉት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዋ፤ ሰነዱ አጠቃላይ የፓርቲውን የምርጫ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ትልቅ ፍኖተ ካርታ መሆኑን ገልጸዋል። የስትራቴጂው ዋና ዓላማ “በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በክልል ምክር ቤቶች በቂ ወንበር ለማሸነፍ የሚያስችለንን ሥራ እንዴት እንደምንሠራ የሚያሳይ ነው” ያሉት ኃላፊዋ፤ ስትራቴጂው በአራት ክፍሎች የተከፈለ መሆኑንም አብራርተዋል። የስትራቴጂው ዋና ዋና ነጥቦች በምርጫው...

የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተስፋና ስጋት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎች እና የመራጮች ምዝገባ የሚያካሄድበትን የዲጂታል ሥርዓት በሀገሪቱ የምርጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚተገበር አስታውቋል። ቦርዱ ይህ ሥርዓት የምርጫ ሂደቱን ለማዘመን፣ ለማቀላጠፍና የጊዜና የጉልበት ብክነትን ለማስቀረት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። በሌላ በኩል በዲጂታል ምዝገባ ስርዓቱ ከታገዘው  የዕጩዎች ምዝገባ ተሞክሯቸው በመነሳት  አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሂደቱ ላይ ያላቸውን ስጋት ይገልጻሉ። ለመሆኑ የዲጂታል የመራጮች ቴክኖሎጂ ምንድን ነው? በምርጫ ሂደት ውስጥ ያሉ ዋና ተዋንያን በተለይም የፖለቲካ ፓርቲዎች ስለሂደቱ ምን አይነት ግምገማ አላቸው? በተለይም ከስርዓቱ አዲስነት፣ በከፊል ከመተግበሩ፣ እንደ ኢንተርኔት ተዳራሽነት ካሉ የመሰረተ ልማት እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ክኅሎት (digital literacy) ክፍተቶች፣ ከሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ እና ከሳይበር ደህንነት ጋር የተያያዙ ስጋቶችስ የትኞቹ ናቸው? የዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ተስፋዎች እንደ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሆነ አዲስ የሚተገበሩት የዲጂታል መመዝገቢያ ቴክኖሎጂዎች መራጮችና እጩዎች በምዝገባ ሂደት ሊያጋጥሟቸው የሚችልን መጉላላት፣ የሚያጠፉትን ጊዜና ጉልበት፣ በምዝገባ ሂደት ሊያጋጥማቸው የሚችልን ማንኛውም ተፅዕኖ ለማስቀረት ያለሙ እንደሆኑ ነው።   በተለይም አካል ጉዳተኞች (ዓይነ-ሥውራን) ራሳቸውን በራሳቸው መመዝገብ እንዲችሉ፣ መራጮች ቋሚ የመራጭነት...

የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በፍርድ ቤት ጊዜያዊ እገዳ ተጣለበት

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ አምስት የምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልል ውጭ ሆነው በቀጥታ የፓርላማ ምርጫ እንዲካሄድባቸው በተላለፈው ውሳኔ ላይ ጊዜያዊ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ። ፍርድ ቤቱ እግዱን ያስተላለፈው ከዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ የቀረበውን የእግድ አቤቱታ ተከትሎ ነው። ስምረት ፓርቲ አቤቱታውን ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው በፕሬዝዳንቱ አቶ ጌታቸው ረዳ በኩል ነው። ዛሬ ሐሙስ የካቲት 19፤ 2018 ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ለቀረበው አቤቱታ ተከሳሽ ወይም ተጠሪ የተደረገው ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑን አቶ ጌታቸው በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ያጋሩት የፍርድ ቤት ሰነድ አመልክቷል።ምርጫ ቦርድ በፍርድ ቤት አቤቱታ የቀረበበት፤ በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል “አከራካሪ ሆነው” የቆዩ የተባሉ አምስት የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ይፋ ባደረገው ውሳኔ ነው። እነዚህ የምርጫ ክልሎች ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኮረም ኦፍላ እና ራያ አላማጣ ናቸው። https://twitter.com/ethioelections/status/2025914790296588598 በአምስቱ የምርጫ ክልሎች የሚደረገው የፓርላማ ምርጫ “በቀጥታ” እንዲሆን እና ለክልል ምክር ቤት መቀመጫዎች የሚደረገው ምርጫ “አመቺ ጊዜ ተመርጦ ወደፊት እንዲካሄድ” በመጀመሪያ የወሰነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት መሆኑን ቦርዱ በወቅቱ አስታውቆ ነበር። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔውን ያስተላለፈው በአማራ...

እናት ፓርቲ በአማራ እና ትግራይ ክልሎች ዕጩዎችን ባያቀርብም “በትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት” ስር ጠንካራ ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀቱን አስታወቀ

እናት ፓርቲ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሊካሄድ በታቀደው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ በትግራይና አማራ ክልሎች በጸጥታ ችግር ምክንያት እጩዎችን ማስመዝገብ አለመቻሉን አስታወቀ። ይሁን እንጂ ፓርቲው "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት" በሚል አዲስ የፓርቲዎች ቅንጅት ማዕቀፍ ከሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በመጪው ምርጫ ተወዳዳሪ ኃይል ለመሆን እንደሚሰራም ገልጿል። የእናት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አቶ ጌትነት ወርቁ ፓርቲያቸው ለመጪው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ ክልሎች ተወዳዳሪ እጩዎችን ማስመዝገቡን አስታውቀዋል። አቶ ጌትነት ‘ለምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር’ እንዳብራሩት፣ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች ግን ፓርቲያቸው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የዕጩዎች የምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ የመጨረሻ ቀነ ገደብ (የካቲት 16 ቀን 2018 ዓ.ም) ድረስ ተወዳዳሪ እጩዎችን ማስመዝገብ አልፈለገም። በሁለቱ ክልሎች በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ፓርቲያቸው ዕጩዎችን ማስመዝገብ አለመፈለጉን የገለጹት አመራሩ፤ ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደቱ ሁሉን አቀፍ እና ሀገራዊ እንዲሆን፣ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈላጊ መፍትሄዎችን በማመንጨትና አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር ሂደቱን መደገፍ እንዳለበት አሳስበዋል። አቶ ጌትነት አክለውም፣ "ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት (ለኢትዮጵያ)" የተሰኘው አደረጃጀትና ቅንጅት በአነስተኛ...

በትግራይ ክልል ስር የነበሩ አምስት የምርጫ ክልሎች “በቀጥታ” ምርጫ እንዲካሄድባቸው ተወሰነ

በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል “አከራካሪ ሆነው” የቆዩ የተባሉ አምስት የምርጫ ክልሎች፤ “የይገባኛል ጥያቄው እስከሚፈታ” ድረስ ከትግራይ ክልል ውጪ ሆነው ለፓርላማ “በቀጥታ” ምርጫ እንዲደረግባቸው ውሳኔ ተላለፈ። ውሳኔ የተላለፈባቸው የምርጫ ክልሎች፤ ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኮረም ኦፍላ እና ራያ አላማጣ ናቸው። እነዚህ ምርጫ ክልሎች ከሁለቱ ክልሎች ውጭ ሆነው ምርጫ እንዲካሄድባቸው ውሳኔ ያሳለፈው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው። ለምክር ቤቱ ውሳኔ መንስኤ የሆነው፤ ጥር 22፤ 2018 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ የተደረገው የምርጫ ክልሎች እና ምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ነው። በዚህ ዝርዝር ላይ በሁመራ ምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎች፤ በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን፣ በሰቲት ሁመራ ወረዳ የሚገኝ እንደሆነ ተጠቅሶ ነበር። በአዲ ረመጽ የምርጫ ክልል የሚገኙ ጣቢያዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ በትግራይ ክልል፣ ምዕራባዊ ዞን፣ በወልቃይት እና ፀገዴ ወረዳዎች ውስጥ ያሉ መሆናቸው በዝርዝሩ ላይ ሰፍሯል። በዚሁ ክልል፣ በተመሳሳይ ዞን ውስጥ እንደሚገኝ በምርጫ ቦርድ ዝርዝር ተጠቅሶ የነበረው የፀለምቲ ምርጫ ክልል፣ በፀለምቲ ወረዳ የሚገኝ መሆኑ በሰነዱ ተመልክቷል። በትግራይ ክልል፣ ደቡብ ዞን ስር ያሉ የምርጫ ክልሎች ሆነው የተጠቀሱት ደግሞ ኦፍላ ኮረም እና አላማጣ...

የኢዜማው መሪ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ  በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወንበር መጋራት አለባቸው ሲሉ አሳሰቡ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ-ኢዜማ መሪ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ሀገርን ለማሻገር መጪው 7ተኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች “ወንበር የሚጋሩበት እንጂ” እንደ በፊቱ ብልጽግና ፓርቲ “99 በመቶ አሸነፍኩ” የሚልበት መሆን እንደሌለበት አሳሰቡ።ኢዜማ ትላንት የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት የዘለቀ “ሀገራዊ ወቅታዊ ሁኔታ እና ምርጫ” በሚል ርዕስ የበይነመረብ ውይይት አካሄዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የውይይት መነሻ አቅራቢ የነበሩት የፓርቲው መሪ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ እንዳሉት ምርጫው በ5 ዓመት አንድ ጊዜ የሚደረግ የሐይማኖታዊ በዓል ክንውን ሳይሆን “ካለንበት የፖለቲካ ውጥንቅጥ የምንወጣበት” ብቸኛው መንገድ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም “በዚህ ምርጫ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወንበር ተጋርተው የሚሻገሩበት እንጂ እንደድሮው ብልፅግና ፓርቲ  99 በመቶ አሸነፍኩ ብሎ መቀጠል ሀገርን ወደ ሚፈለገው እድገት አያሻግርም” በማለት አሳስበዋል። ኢዜማ ለህዝብ ክፍት ባደረገው የበይነመረብ (የዙም) ውይይት ከደጋፊዎቹና ከተሳታፊዎች ለተነሱት በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የድርጅቱ መሪና የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ  ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። “የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስቀደም ተቀዳሚ ተግባራችን ነው” ያሉት ፕሮፌሰሩ 50 ዓመታት የመጣንበትን አስከፊ  የብሔር ፖለቲካ  ልምምድ ለመጣል ምርጫ ወሳኙ መንገዳችን...

የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክት ይፋ ማድረጊያ ሥነ ስርዓት ላይ ዕጩዎች የሥነ ምግባር ደንብ ፈረሙ

‎‎የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለመወዳደር የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ምልክት ማስተዋወቂያና የዕጩዎች ሥነ ምግባር ደንብ መፈራረሚያ መርሐ ግብርን ዛሬ የካቲት 14 ቀን 2018 ዓ.ም አካሄደ። በመርሐ ግብሩ የመክፈቻ ንግግራቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት የዕለቱ ትልቅ ሁነት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚወዳደሩባቸውን ምልክቶች ይፋ ማድረግና ለሕዝብ ማስተዋወቅ እንደሆነ ገልጸዋል። የምርጫ ምልክት ይፋ የማድረግያ መርሐ ግብሩ ዋና ዓላማ መራጩ ሕዝብ የሚመርጠውን ለይቶ ማወቅ እንዲችል ከምርጫ ምልክቱ ጀምሮ መረዳትና ማወቅ ስላለበት መሆኑንም ሜላትወርቅ ገልጸዋል። “በተለይም ሚዲያዎች የፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት አካታችና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንድታስተዋውቁና እንድታሳዩ ይጠበቅባቹሃል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ በመርሐ ግብሩም ቦርዱ በ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የሚካፈሉና እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ  48 የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመወዳደሪያ ምልክትና ስያሜን በቅደም ተከተል በተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም የዕጩዎች ሥነ ምግባር ደንብ መፈራረሚያ መርሐ ግብር ተያይዞ ተካሄዷል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሜላትወርቅ  “የሠለጠነ ምርጫ ለማካሄድ ሥርዓትና ደንብ ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህ በምርጫው የሚወዳደሩ ዕጩዎችና ፓርቲዎች የሥነ ምግባር ደንቡን መፈረማቸው አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የዕጩዎች ሥነ...