በባልደራስ ይፋዊ ማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ የወጣውን መግለጫ፣ ፕሬዚዳንቱ አላውቀውም አሉ
የባልደራስ ፓርቲ "የሥራ አስፈፃሚ እና የምክር ቤት አባላት" ባወጡት መግለጫ፣ በፓርቲው ፕሬዚዳንት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች የፓርቲውን መዋቅርና መተዳደሪያ ደንብ የጣሱ ናቸው ሲሉ ወቀሱ፤ የፓርቲው ፕሬዚዳንት በበኩላቸው መግለጫው የወጣበት የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ከፓርቲው ቁጥጥር ውጪ ሆኗል...
መድረክ ለምርጫ የሚወዳደረው ለተሳትፎ ያህል ብቻ እንደሆነ ሊቀ መንበሩ አቶ አምዶም ገብረሥላሴ ገለጹ
የአራት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በዘንድሮው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደረው ለተሳትፎ ያህል መሆኑን የግንባሩ ሊቀመንበር አቶ አምዶም ገብረሥላሴ ለ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸዋል።
መድረክ ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲ እና ሉዓላዊነት፣ የኦሮሞ...
ኢዜማ በ“ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘገባ ላይ ያቀረበው ቅሬታ
“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትላንት ሐሙስ፣ መጋቢት 16፤ “ገዢው ፓርቲ የኢዜማ መሪና ምክትላቸው ለፓርላማ በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ” በሚል ርዕስ ለንባብ ላበቃው ዜና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ያቀረበው ቅሬታ ሙሉ...
በአማራ እና ትግራይ ክልሎች “አከራካሪ” አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባ አልተጀመረም
ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች “አከራካሪ” በተባሉት አምስቱ የምርጫ ክልሎች፡- ሁመራ፣ አዲ ረመጽ፣ ጠለምት፣ ኦፍላ ኮረም እና አላማጣ የምርጫ ክልሎች ውስጥ ያሉ አካባቢዎች የመራጮች ምዝገባን ጨምሮ ምንም ዓይነት የምርጫ እንቅስቃሴ እየተካሄደ አለመሆኑን...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቁሳቁሶች እሸጋ መርሀ ግብርን ለመገናኛ ብዙኃን አባላት አስጎበኘ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ሀገራዊ ምርጫንና በተለይም የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ አስፈላጊ የሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶችን የእሸጋ መርሃ ግብር በመጪዉ አሁድ እንደሚያጠናቅቅ ገለጸ። ቦርዱ ዛሬ የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በየኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነትና የሎጂስቲክስ አገልገሎት...
በድሬዳዋ ከ47 የከተማ ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች ውስጥ ብልፅግና በ32ቱ ብቻውን ይወዳደራል
“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ያደረገው የ7ተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ዝርዝር ሰነድ እንደሚያሳየው፣ የድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት ካሉት 47 የምርጫ ክልሎች ውስጥ፣ በ32ቱ ብልፅግና ብቻውን እንደሚወዳደር ተረድታለች።
የድሬዳዋ ከተማ...
ገዢው ፓርቲ የኢዜማ መሪና ምክትላቸው ለፓርላማ በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ
የአዲስ አበባ ከተማ ካሉት 23 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች መካከል ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በሦስት የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ። ብልጽግና ፓርቲ ዕጩዎቹን ካላቀረበባቸው የምርጫ ክልሎች ሁለቱ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መሪ እና...
የአብን የፓርላማ አባሉ ዶ/ር አበባው ደሳለው በመጪው ምርጫ ኢሕአፓን ወክለው ሊወዳደሩ ነው
በሰኔ 2013 ዓ.ም በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን ወክለው የፓርላማ አባል የሆኑት ዶ/ር አበባው ደሳለው፤ በመጪው ምርጫ ኢሕአፓን ወክለው ሊወዳደሩ ነው። የአብን የአዲስ አበባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የነበሩት ዶ/ር ይህዓለም ታምሩም በተመሳሳይ መልኩ...
የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በፍርድ ቤት ጊዜያዊ እገዳ ተጣለበት
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ አምስት የምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልል ውጭ ሆነው በቀጥታ የፓርላማ ምርጫ እንዲካሄድባቸው በተላለፈው ውሳኔ ላይ ጊዜያዊ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ። ፍርድ ቤቱ እግዱን ያስተላለፈው ከዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ የቀረበውን የእግድ አቤቱታ ተከትሎ...
ፓርቲ የሚቀያይሩት የሐረሩ ፖለቲከኛ ተስፋሁን ምልኬ
ከሰሞኑ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢሶዴፓ ዕጩዎች መሰረዛቸውን ካሳወቀ ቀናት ብኋላ፣ “ከምርጫው ራሴን ከዕጩነት አግልያለሁ፤ ከኢሶዴፓ አባልነት፣ አመራርነትም መልቀቄን በደብዳቤ አስገብቻለሁ” የሚል መልዕክት በቲክቶክ ገጻቸው በማስተላለፍ ከአምስተኛው የፖለቲካ ፓርቲያቸው በገዛ ፈቃዳቸው መሰናበታቸውን አሳውቀዋል።










