የምርጫ 2018 ዕጩዎች ስብጥር፤ በቁጥር እና በምስላዊ መግለጫ
ግንቦት 19፣ 2018 (ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)፤ የ7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ በመጪው ሰኞ፣ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለማካሄድ የሚያስችሉ የመጨረሻ ምዕራፍ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ ሰነዶች እንደሚያመላክቱት፣ ምርጫው ከትግራይ...
ገዢው ፓርቲ የኢዜማ መሪና ምክትላቸው ለፓርላማ በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ
የአዲስ አበባ ከተማ ካሉት 23 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች መካከል ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በሦስት የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ። ብልጽግና ፓርቲ ዕጩዎቹን ካላቀረበባቸው የምርጫ ክልሎች ሁለቱ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መሪ እና...
የምርጫ አስፈፃሚዎች ክፍያቸው በመዘግየቱ “ራሳችንን ለእንግልት አሳልፈን ሰጥተናል” ሲሉ አማረሩ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀጠራቸው ጊዜያዊ የምርጫ አስፈጻሚዎች ቀሪው 60 በመቶ ክፍያቸው እና የመራጮች ምዝገባ በተራዘመባቸው 14 ቀናት ሊታሰብላቸው የሚገባው ሙሉ አበል እንዳልተከፈላቸው በመግለጽ ቅሬታ አቀረቡ። ምርጫ ቦርድ በበኩሉ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ቀሪው ክፍያ እንዲፈጸምላቸው መጀመሪያ...
ገዢው ብልፅግና ፓርቲ ለ64 የፓርላማ መቀመጫዎች ብቻውን ለምርጫ መቅረቡ ታወቀ
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመለከተ። ከእነዚህ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አርባ ስድስቱ በኦሮሚያ፣ አስራ...
የብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ ዕጩ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተተኩ
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል በአዲስ አበባ ከተማ ለፓርላማ አባልነት ዕጩ ሆነው ቀርበው የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተተኩ። ዶ/ር ሳሙኤል ከምርጫው ራሳቸውን ያገለሉት “በግል ምክንያት” እንደሆነ ለ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በ7ተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ስንት የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎች ወይም የግል ተወዳዳሪዎች ፓርላማ ሊገቡ ይችላሉ?
(ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) ነገ፣ ግንቦት 24፣ 2018 በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ፣ ለፓርላማ ምርጫ የሚካሄድባቸው የፓርላማ ወንበሮች 501 መሆናቸው ታውቋል፤ ይህም የሆነው የትግራይ 38 እና የአማራ 8 ወንበሮች ምርጫ ስለማይካሄድባቸው ነው። ብልፅግና ፓርቲ...
ኢዜማ በ“ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘገባ ላይ ያቀረበው ቅሬታ
“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትላንት ሐሙስ፣ መጋቢት 16፤ “ገዢው ፓርቲ የኢዜማ መሪና ምክትላቸው ለፓርላማ በሚወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ሳያቀርብ ቀረ” በሚል ርዕስ ለንባብ ላበቃው ዜና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ያቀረበው ቅሬታ ሙሉ...
በሲዳማ ክልል ሰባት ፓርቲዎች ሲፎካከሩ፣ በአምስት ክልሎች ብልፅግና በብቸኝነት መንግሥት መመሥረት የሚያስችል የዕጩዎች ቁጥር...
በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ፣ ለክልል ምክር ቤቶች የሚቀርቡ ዕጩዎችን ዝርዝር “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት አጠናቅራዋለች። በዚህ የዕጩዎች መረጃ መሠረት...
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ የታዋቂ ፖለቲከኞች የምርጫ...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ውጤት የማረጋገጥ ሂደቱን በመቀጠል፣ የ723 የምርጫ ክልሎችን ውጤት ማፅደቁን ዛሬ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ።
ቦርዱ በ3 ዙር ካወጃቸው ውጤቶች በተጨማሪ ዛሬ የ40 የሕዝብ...
በዛሬው የምርጫ ውጤት እወጃ ከሁለት እስከ ስድስት አሐዝ የተራራቀ ድምፅ ያገኙ ዕጩዎች አሸናፊነታቸው ፀደቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ውጤት የማረጋገጥ ሂደቱን በመቀጠል፣ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ምሽት በስካይላይት ሆቴል በሰጠው ዕለታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ተጨማሪ የጸደቁ ውጤቶችን ይፋ አደረገ ።
ዛሬ ውጤታቸው ከተነገሩ ተመራጮች መካከል ከፍተኛውን...










