ፓርቲ የሚቀያይሩት የሐረሩ ፖለቲከኛ ተስፋሁን ምልኬ
ከሰሞኑ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢሶዴፓ ዕጩዎች መሰረዛቸውን ካሳወቀ ቀናት ብኋላ፣ “ከምርጫው ራሴን ከዕጩነት አግልያለሁ፤ ከኢሶዴፓ አባልነት፣ አመራርነትም መልቀቄን በደብዳቤ አስገብቻለሁ” የሚል መልዕክት በቲክቶክ ገጻቸው በማስተላለፍ ከአምስተኛው የፖለቲካ ፓርቲያቸው በገዛ ፈቃዳቸው መሰናበታቸውን አሳውቀዋል።
በሲዳማ ክልል ሰባት ፓርቲዎች ሲፎካከሩ፣ በአምስት ክልሎች ብልፅግና በብቸኝነት መንግሥት መመሥረት የሚያስችል የዕጩዎች ቁጥር...
በመጪው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ፣ ለክልል ምክር ቤቶች የሚቀርቡ ዕጩዎችን ዝርዝር “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት አጠናቅራዋለች። በዚህ የዕጩዎች መረጃ መሠረት...
‘ሥራችንን ብናስረክብም ደሞዝ እና አበል እየተከፈለን አይደለም’ በሚል የምርጫ አስፈፃሚዎች አማረሩ
በመራጮች ምዝገባ ሂደት ላይ ተሰማርተው የነበሩ የምርጫ አስፈፃሚዎች፣ ሥራቸውን በአግባቡ አጠናቀው ቢያስረክቡም የክፍያ መዘግየት ቅሬታ እንደፈጠረባቸው “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተቻቸው የአቤቱታ ደብዳቤዎች አመላከቱ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ “አጠቃላይ በውሉ ያስመዘገቡት መረጃ ላይ...
ገዢው ብልፅግና ፓርቲ ለ64 የፓርላማ መቀመጫዎች ብቻውን ለምርጫ መቅረቡ ታወቀ
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመለከተ። ከእነዚህ የምርጫ ክልሎች ውስጥ አርባ ስድስቱ በኦሮሚያ፣ አስራ...
‘የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ’ የመራጮች ምዝገባ ግኝት
ኅብረቱ በ4,396 (83 በመቶዎቹ ማኑዋል እና 27 በመቶዎቹ ዲጂታል) የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ 522 ታዛቢዎችን ማሰማራቱን ያሳወቀ ሲሆን፣ 1,410 (32%) ጣቢያዎች ውስጥ ቢያንስ አንድ ጊዜ የምዝገባ ሂደቱ ተቋርጦ ነበር። በተጨማሪም፣ በሕግ ያልተፈቀዱ ቦታዎች ላይ የተቋቋሙ ጣቢያዎች፣...
በባሕር ዳር ከተማ የምርጫ ቅስቀሳ መቀዛቀዙ ተገለጸ
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በባሕር ዳር ከተማ የጎዳና ላይ ቅስቀሳዎችን እስካሁን አለመጀመራቸውን “ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተመልክታለች። የመራጮች ምዝገባ ከተጠናቀቀ በኋላ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰፊ እንቅስቃሴ...
አቶ ዳውድ ኢብሳ በ “ፀጥታ ስጋት” ምክንያት በዘንድሮው ምርጫ እንደማይወዳደሩ ኦነግ አስታወቀ
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ፕሬዝዳንት አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት በ7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ በዕጩነት እንደማይወዳደሩ ድርጅቱ ገለጸ።
የኦነግ የዲሲፒሊን እና ቁጥጥር ኮሚቴ ሊቀመንበር አቶ አለማየሁ ዲሮ ለ “ምርጫ 2018...
116 የምርጫ ጣቢያዎች ክልከላ በተደረገባቸው ወታደራዊ፣ ፖሊስ፣ ሃይማኖት ተቋማት እና መጠጥ ቤቶች ተቋቁመው መገኘታቸውን...
የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ ትናንት ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ በመራጮች ምዝገባ ላይ የታዩ አዎንታዊ እና አሉታዊ ኹነቶችን ገልጿል።
በዚህም ኅብረቱ ታዛቢዎችን ካሠማራባቸው 4,396 የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በ102 የማኑዋል ምዝገባ ጣቢያዎች እና 14 የዲጂታል ምዝገባ ጣቢያዎች፣...
“የበጀት እጥረት” ያቀዛቀዘው የሐረር ከተማ የምርጫ ድባብ
በሐረር ከተማ የመስክ ቅኝት ለማድረግ የተንቀሳቀሰው የ“ምርጫ 2018 - ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ዘጋቢ፣ በከተማዋ የምርጫው ድባብ ካለፉት ምርጫዎች አንፃር መቀዛቀዙን አስተውሏል።
ይህንን አስመልክቶ ጥያቄ ያቀረበላቸው ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት...
ዶ/ር ራሔል ባፌ ኢሶዴፓ ያስመዘገባቸው 309 ዕጩዎች መሰረዛቸውን በመቃወም ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና ፓርላማ...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) በጻፈው ደብዳቤ፣ ፓርቲው ለ7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ያቀረባቸው ዕጩዎች ከውድድር ውጪ መደረጋቸውን አስታውቋል። ቦርዱ ይህን ውሳኔ ያስተላለፈው በፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሔል ባፌ አማካይነት የተመዘገቡት ዕጩዎች...










